3 አዳዲስ ቅርንጫፎች ተከፈቱ
ቡና ባንክ የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት ሶስት አዳዲስ ቅርንጫፎች በመጨመር የቅርንጫፎቹን ቁጥር ወደ 271 አሳድጓል።
የሁሉም ኢትዮጲያዊ የሆነው ቡና ባንክ ሁሉንም የኢትዮጲያ ክፍል በአገልግሎት በማዳረስ የደንበኞቹን ቁጥር ለማስፋት የጀመረውን ግስጋሴ አጠናክሮ ቀጥሏል።
በዚህ መሰረትም ማራኪ ቅርንጫፍ በጎንደር፣ ባልጪ ቅርንጫፍ በሰሜን ሸዋ ምንጃር እንዲሁም ቡልጋ ቅርንጫፍ ሰሜን ሸዋ ሀገረማሪያም ከፍቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
268ኛ ቅርንጫፍ ተከፈተ
ቡና ባንክ በደቡብ ኢትዮጲያ የጀመረውን አገልግሎት ማስፋፋት አጠናክሮ በመቀጠል ዱራሜ ከተማ ላይ 268ኛውን ቅርንጫፉን ከፍቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ዱራሜ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ከንባታ ጠንባሮ ዞን ውስጥ የምትገኝ ከተማ ናት። ቡና ባንክ በዚህች ከተማ ቀበሌ 02 አካባቢ ቅርንጫፉን ሲከፍት ለአካባቢው ማህበረሰብ የሚሰጠውን አገልግሎት በጥራት ለማስቀጠልና የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ራዕይ ሰንቆ ነው።
267ኛ ቅርንጫፍ ተከፈተ
ባንኩ ለባልደራስና አካባቢው ነዋሪዎች አገልግሎቱን ለመስጠት 267ኛ ቅርንጫፉን “ባልደራስ ቅርንጫፍ” ብሎ በመሰየም ለአገልግሎት ክፍት አድርጎ ስራ ጀምሯል።
ባልደራስ ቅርንጫፍ በአዲስ አበባ ከተማ የካ ክፍለከተማ ይገኛል፡፡
266ኛ ቅርንጫፍ ተከፈተ
የቅርንጫፍ ቁጥሮቹን በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመር ላይ የሚገኘው ቡና ባንክ “እሪበከንቱ ቅርንጫፍ”ን የባንኩ 266ኛ ቅርንጫፍ አድርጎ ከፍቷል፡፡ ቅርንጫፉ በአዲስ አበባ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ይገኛል፡፡