Bunna Bank

እጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን ጥቆማ ለመቀበል የወጣ ማስታወቂያ

ለቡና ባንክ አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

እጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን ጥቆማ ለመቀበል የወጣ ማስታወቂያ

የቡና ባንክ አ.ማ የባላክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ ህዳር 30 ቀን 2016 ባካሄደው 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ያቋቋመው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማና አስመራጭ ኮሚቴ ከሰኔ 01 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ጥቆማ በመቀበል ላይ የሚገኝ ሲሆን የቦርድ አባላትን ለመጠቆም የሚያስችለውን የጥቆማ መሙያ ቅጽ በቡና ባንክ አ.ማ ድረ ገጽ https://www.bunnabanksc.com ወይም የባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት በሚገኝበት ቦሌ መንገድ ሩዋንዳ መታጠፊያ አካባቢ ባለው የቡና ባንክ አ.ማ ሕንፃ 8 ፎቅ በሚገኘው የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ ጽ/ቤት ቢሮ ወይም በባንኩ ቅርንጫፎች ማግኘት ይቻላል፡፡

ስለሆነም ባለአክሲዮኖች ለዳይሬክተሮች የቦርድ አባልነት ብቁ የሆኑትን ለባንኩ ሁለንተናዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችሉትን እና ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉትን እጩዎች በቅጹ ላይ በጥንቃቄ በመሙላት እስከ ጳጉሜ 05 ቀን 2016 ዓ.ም  ድረስ ብቻ ከላይ በተገለፀው የኮሚቴው ጽ/ቤት በአካል በማቅረብ ወይም አድራሻውን ለቡና ባንክ አ.ማ የዳይሬክተሮች ቦርድ  አባላት ጥቆማ አስመራጭ ኮሚቴ በማለት በባንኩ የፓ.ሣ.ቁጥር 1743 ኮድ 1110  በአደራ ደብዳቤ መላክ ወይም የተሞላውን ቅፅ ስካን በማድረግ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው በባንኩ ኢሜል bibnomination@bunnabanksc.com አያይዘዉ መላክ የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ተጠቋሚ እጩ የቦርድ አባላት የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፤

  1. የባንኩ ባላክሲዮን የሆነ/ነች
  2. እድሜው 30 ዓመት  በላይ የሆነ/ነች
  3. የዳይሬክተሮች የቦርድ አባል ሆኖ/ሆና ቢመረጥ/ብትመረጥ ለመሥራት ፈቃደኛ የሆነ/ች፣
  4. ከታወቀ የከፍተኛ የትምህርት ተቋም ቢያንስ የመጀመሪያ ዲግሪ ያጠናቀቀ/ች፣
  5. የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ስብስብ በባንክ ሥራ፤ በፋይናንስ፤ በአካውንቲንግ፤በማኔጅመንት፤ በኢኮኖሚክስ፤በህግ፤በቢዝነስ አስተዳደር፤በኦዲቲንግ፤በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ወይንም በኢንቨስትመንት ማኔጅመንት መሰረታዊ ክህሎትን /ችሎታን ያካተተና የጾታ ስብጥርን ያገናዘበ  ቢሆን ይመረጣል፣
  6. የፋይናንስ ድርጀት የቦርድ ዳይሬክተር ያልሆነ/ነች ወይም ዳይሬክተሩ/ሯ 10% ወይም  ከዚያ በላይ የባለቤትነት ድርሻ ያልያዘበት/ችበት የንግድ ድርጅት፤
  7. የማንኛውም ባንክ ተቀጣሪ ሠራተኛ ያልሆነ/ነች፤
  8. የቡና ባንክ አ.ማ የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ አባል ያልሆነ/ነች፤
  9. በግሉ/ሏ ወይም ሌላ ባላክሲዮንን በመወከል በቡና ባንክ አክሲዮን ማህበርን ለስድስት ዓመታት በቦርድ አባልነት አገልግሎ/ላ የለቀቀበት/ቀቀችበት ጊዜ ጀምሮ ስድስት ዓመታት ያለፈው/ያለፋት፤
  10. በብሄራዊ ባንክ እምነት መሰረት ታማኝ፤ሐቀኛ ጠንቃቃና መልካም ዝና ያለው/ያላት፤
  11. መልካም የፋይናስ ታሪክና አቋም ያለው/ያላት፤ የንግድ ስራ ከመተግበር ወይም ድርጅትን ከመምራት አኳያ በፍርድ ቤት የመክሰር ውሳኔ ያልተላለፈበት/ባት፤ ከታክስና ከባንክ ክፍያዎች ጋር በተያያዘ ግዴታዎቹን/ቿን በአግባቡ የተወጣ/ች፤
  12. መልካም ስነምግባር ያለው/ያላት ፤ከዚህ በፊት በንግድ ማህበር አደራጅነት ዳይሬክተርነት ፤ስራ አስኪያጅነት፤ ተቆጣጣሪነት ኦዲተርነት፤ ወይም በሌላ የአመራር ኃላፊነት ላይ ተመድቦ/ባ ሲሰራ/ስትሰራ ኃላፊነቱ/ቷ ጋር በተያያዘ ወይም በማናቸውም ሌላ ሁኔታ በኢትዮጲያ ውስጥም ሆነ ከኢትዮጲያ ውጭ በእምነት ማጉደል፤ በስርቆት፤ በማጭበርበር፤ በውንብድና፤ ወይም በሌላ ለቦርድ አባልነት ብቁ በማያደርግ ተመሳሳይ ወንጀል በፍ/ቤት ተከሶ/ሳ የጥፋተኝነት ውሳኔ ያልተሰጠበት/ባት፤
  13. ከመንግስት ባለስልጣናት መረጃን በመደበቅ የተሳሳቱ የሂሳብ ወይም ሌሎች ሰነዶችን በመስጠት የተቆጣጣሪ አካላትን  ማረጋገጫዎች ባለመቀበል መስፈርቶችን ባለማሟላት የርምት ወይም የማስተካካያ እርምጃዎችን ባለመውሰድ ሪከርድ የሌለበት/ባት፤
  14. በኢትዮጲያ ውስጥም ሆነ በውጭ  ሀገር በሚገኝ በማናቸውም በፈረሰ ባንክ ውስጥ ዳይሬክተር የነበረ/ረች ከሆነ በቅድሚያ በብሔራዊ ባንክ የፅሁፍ ፈቃድ ማቅረብ የሚችል/ምትችል ፤
  15. ዕጩ ተጠቋሚው በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው ድርጅት ከሆነ ድርጅቱን ወክሎ የሚያገለግል ተጠቋሚ ተወካይ (ጠተፈጥሮ ሰው) መመደብ ያለበት ሲሆን ይህ ተወካይ ሁሉንም መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅበታል፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር በ011-1-264357 በመደወል ባለአክሲዮኖች ማብራሪያ ማግኘት ይችላሉ፡፡

ማሳሰቢያ፤

አስመራጭ ኮሚቴው ከጳጉሜ 05 ቀን 2016 ዓ.ም በኋላ የሚቀርቡ ጥቆማዎችን የማይቀበል መሆኑን ከወዲሁ ያሳስባል፡፡

 የቡና ባንክ አ.ማ

የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት አስመራጭ ኮሚቴ

[ivory-search id="5747" title="Custom Search Form"]

This will close in 0 seconds

error: