Bunna Bank

ለቡና ባንክ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን በቁጥር 1047/2017 ባወጣው መመሪያ መሰረት የባለአክሲዮኖች የአክሲዮን ባለቤትነት ምስክር ወረቀት ወደ ኤሌክትሮኒክ የባለቤትነት ማረጋገጫ መቀየር  እና  የባለአክሲዮኖች መረጃ ወደ ማዕከላዊ የሠነደ ሙዓለ ንዋዮች ግምጃ ቤት  መላክ እንዳለበት ተደንግጓል፡፡  በመሆኑም የወጣውን አስገዳጅ መመሪያ ለመፈጸም እንዲቻል የቡና ባንክ ባለአክሲዮኖች (ግለሰቦች ) የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ካርድ ኮፒ፣ የፋይዳ ካርድ ቁጥር (FAN)፣ የትውልድ ቀን(እ.ኤ.አ) ፣ አድራሻ (ክልል፣ ክ/ከተማ፣ ወረዳ/ቀበሌ፣ የቤት ቁጥር፣ ተንቀሳቃሽ ስልክ ቁጥር፣ ኢ-ሜል) ፣የታክስ መክፈያ መለያ ቁጥር (TIN)፤  ባለአክሲዮኑ ሕጋዊ ሰውነት ያለው ድርጅት ከሆነ የምዝገባ ቁጥር ፣  የታክስ መክፈያ መለያ ቁጥር (TIN) ፣ ሙሉ አድራሻ እና  የወኪሉ ሰው ሙሉ መረጃ በዋናው መ/ቤት 6ኛ ፎቅ አክሲዮን አስተዳደር ክፍል ወይም በአቅራቢያዎ በሚገኝ የቡና ባንክ ቅርንጫፍ እስከ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. በመቅረብ እንዲሰጡ  በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

ቡና ባንክ
የባለራዕዮች ባንክ

This will close in 0 seconds

Open Your Bank Account Today!

አካውንት ይክፈቱ የክፍያ ካርድዎን ያዝዙ ፣ ፈጣን አገልግሎት ማግኘት ይጀምሩ! ዛሬውኑ ይቀላቀሉን!

Open Bunna Account

You cannot copy content of this page