Bunna Bank

Solomon mekbib

ቡና ባንክ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) የሰነደ ሙአለነዋይ ምዝገባውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ

(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17 ቀን፣ 2018 ዓ.ም.) ቡና ባንክ አ.ማ. የሰነደ ሙአለነዋይ ምዝገባን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) ፈቃድ ማግኘቱን በደስታ ይገልጻል። ይፋዊ ምዝገባው ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህም ስኬታማ ምዝገባ በባንኩ የኮርፖሬት እድገት እና እየተስፋፋ ባለው የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ውስጥ ትልቅ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው። በዚህ ኦፊሴላዊ ምዝገባ መሰረት የቡና ባንክ አ.ማ. 61,895,598 ነባር መደበኛ አክሲዮኖች፣ እንዲሁም ለነባር ባለአክሲዮኖች የሚቀርቡ 2,587,002 አዳዲስ መደበኛ አክሲዮኖች በባለስልጣኑ ጸድቀዋል፡፡ ይህ ስኬት ቡና ባንክ በኢትዮጵያ የሰነደ ሙአለነዋይ ገበያ (ESX) ውስጥ በቀጣይ ለመሳተፍ ላስቀመጠው እቅድ ወሳኝ እርምጃ ነው። ባንኩ ለግልጽነት፣ ለጠንካራ የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ለባለአክሲዮኖቹ ዘላቂ እሴት ለመፍጠር ያለውን ጠንካራ ቁርጠኝነት ያጎላ ተግባር ነው። የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሙሉጌታ ዓለማየሁ በሰጡት መግለጫ”የሰነደ ሙአለነዋያችንን በካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) በተሳካ ሁኔታ ማስመዝገባችን ለቡና ባንክ የሚያኮራ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው። ይህ ስኬታማ ክንውን የባንካችንን የወደፊት ስትራቴጂያዊ አቅጣጫ የሚያንጸባርቅ፣ የገቨርናንስ ደረጃችንን የሚያሳድግ እና የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ እያደገ ሲመጣ ለባለአክሲዮኖቻችን አዳዲስ እድሎችን የሚከፍት ነው። በዚህ ረገድ ባለአክሲዮኖቻችን እና ባለድርሻ አካላት ላሳዩን ቀጣይነት ያለው እምነት እና ድጋፍ ጥልቅ ምስጋናችንን እናቀርባለን።” ባንኩ እንዳስታወቀው ከዚህ የአክሲዮን ጉዳይ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ መረጃዎችና ማብራሪያዎች በሂደት በይፋ የሚገለጹ ይሆናል። በዚህ አጋጣሚ ቡና ባንክ ለኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ ለክቡራን ባለአክሲዮኖቹ፣ ለደንበኞቹ እና ለሁሉም አጋሮቹ ላደረጉት የማያቋርጥ ድጋፍ የከበረ ምስጋናውን ያቀርባል። ይፋዊ የአክሲየን ማህበሩን መግለጫ ሰነድ (Prospectus) ከዚህ በታች የሚገኘው ማስፈንጠሪያ በመጫን አውርደው ማንበብ ይችላሉ፡፡ 📄 መግለጫውን ያውርዱ (PDF) ለተጨማሪ መረጃ፣ እባክዎ ያነጋግሩን፦ ስልክ፦ 8501 Bunna Bank Successfully Completes Securities Registration with the Ethiopian Capital Market Authority (ECMA) (Addis Ababa, June 24, 2026) Bunna Bank S.C. is delighted to announce that it has received approval from the Ethiopian Capital Market Authority (ECMA) to register its securities. The formal registration was completed on June 23, 2026, marking a significant milestone in the Bank’s corporate development and Ethiopia’s evolving capital market. Under this registration, 61,895,598 existing ordinary shares, and the issuance of up to 2,587,002 new ordinary shares to be offered to existing shareholders, have been approved. This achievement represents an important step toward Bunna Bank’s planned participation in the Ethiopian Securities Exchange (ESX). It underscores the Bank’s strong commitment to transparency, robust corporate governance, and the creation of long-term value for its shareholders. Chief Executive Officer of Bunna Bank S.C., Ato Mulugeta Alemayehu, in his statement, stated: “The successful registration of our securities with the ECMA is a proud milestone for Bunna Bank. It reflects our forward-looking strategy, enhances our governance standards, and opens new opportunities for our shareholders as Ethiopia’s capital market matures. We remain deeply grateful to our shareholders and stakeholders for their continued trust and support.” Download the Prospectus using the link below: 📄 Download the Prospectus (PDF) Further information regarding the share management and related issues will be communicated officially in due course. At this juncture in time, Bunna Bank would like to express its sincere appreciation to the Ethiopian Capital Market Authority, its valued shareholders, customers, and all partners for their unwavering support. For more information, please contact: Telephone: 8501

ቡና ባንክ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) የሰነደ ሙአለነዋይ ምዝገባውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ Read More »

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለፀሎተ ሀሙስ በሰላም አደረሳችሁ፡፡

ለበዓል ከዉጪ ሀገር የተላከሎትን ገንዘብ በባንካችን ይመንዝሩ፤ ጠቀም ያለ ጉርሻ ያግኙ!! ቡና ባንክ- የባለራዕዮች ባንክ BunnaBank #Chrstianity #Orthodox #Holiday #Foryou #Forex #Bonus

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለፀሎተ ሀሙስ በሰላም አደረሳችሁ፡፡ Read More »

እየመጣን ነው 🚀

የላቀ የዲጂታል ተሞክሮን ከቀልጣፋ አገልግሎት ጋር አጣምረን ይዘንልዎ እየመጣን ነው። በጣትዎ ጫፍ የሚዘወር፣ የባንክ አገልግሎትን መልክ የሚቀይር፤ አዲስ ብስራት፣ ልዩ ነገር… ይዘን ከች ልንል ከደጃፍዎ ደርሰናል! ዝግጁ ነዎት? በቅርብ ቀን ይጠብቁን! ቡና ባንክ- የባለራዕዮች ባንክ #Bunnabank #ComingSoon #StayTuned #SomethingNew #BigUpdate  #SmartBanking #DigitalBanking

እየመጣን ነው 🚀 Read More »

በቅርብ ቀን!

የጊዜን ዋጋ ያከበረ፣ ምቾትዎን ወደ አዲስ ከፍታ የሚያሸጋግር የዲጂታል ሽግግር! 🚀 የባንክ አጠቃቀም ልምድዎን በዘመናዊ ጥበብ የሚቀይር ድንቅ ፈጠራ ይዘን በቅርብ ቀን እንመጣለን። ይጠብቁን፤ #ቡናባንክ #የዲጂታል_አብዮት #ዘመናዊነት #በቅርብ_ቀን #BunnaBank #FinTech #Innovationk

በቅርብ ቀን! Read More »

የባንክ ሒሳብዎን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር አስተሳስረዋል?

ውድ የባንካችን ደንበኞች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው መመርያ መሠረት ሁሉም ደንበኞች የባንክ አገልግሎት ለማግኘት የፋይዳ ቁጥራቸውን ከባንክ ሒሳብ ቁጥር ጋር እስከ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ማጣመር እንዳለባቸዉ ተገልጿል። በመሆኑም ማፈንጠሪያዉን በመጫን https://verifayda.bunnabanksc.com የቡና ባንክ ሒሳብዎን በቀላሉ ከቤትዎ ሆነዉ እንዲያስተሳስሩ ወይም አቅራቢያዎት ወደሚገኝ ቅርንጫፍ በመሔድ እንዲያስተሳስሩ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ ለበለጠ መረጃ ወደ ጥሪ ማዕከላችን 8501 ይደዉሉ፡፡ ቡና ባንክ- የባለራዕዮች ባንክ

የባንክ ሒሳብዎን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር አስተሳስረዋል? Read More »

ዒድ ሙባረክ! 🌙

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ቡና ባንክ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ ልባዊ ምኞቱን ይገልጻል። በዓሉ “ሙባረክ ወመይሙን” የሆነ የሰላም፣ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆንላችሁ፤ እንዲሁም ከቤተሰብ እና ከወዳጅ ዘመዶቻችሁ ጋር በበረካ የተሞላ የደስታ ጊዜ እንድታሳልፉ ከልብ እንመኛለን። ዒድ ሙባረክ! መልካም በዓል! ኻዲም ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት #EidMubarak #EidAlFitr1447 #BunnaBank #Khadim #InterestFreeBanking #Ethiopia #ዒድ_ሙባረክ #ቡና_ባንክ #የተባረከ_በዓል

ዒድ ሙባረክ! 🌙 Read More »

This will close in 0 seconds

Open Your Bank Account Today!

አካውንት ይክፈቱ የክፍያ ካርድዎን ያዝዙ ፣ ፈጣን አገልግሎት ማግኘት ይጀምሩ! ዛሬውኑ ይቀላቀሉን!

Open Bunna Account

You cannot copy content of this page