ቡና ባንክ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) የሰነደ ሙአለነዋይ ምዝገባውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ
(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17 ቀን፣ 2018 ዓ.ም.) ቡና ባንክ አ.ማ. የሰነደ ሙአለነዋይ ምዝገባን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) ፈቃድ ማግኘቱን በደስታ ይገልጻል። ይፋዊ ምዝገባው ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህም ስኬታማ ምዝገባ በባንኩ የኮርፖሬት እድገት እና እየተስፋፋ ባለው የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ውስጥ ትልቅ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው። በዚህ ኦፊሴላዊ ምዝገባ መሰረት የቡና ባንክ አ.ማ. 61,895,598 ነባር መደበኛ አክሲዮኖች፣ እንዲሁም ለነባር ባለአክሲዮኖች የሚቀርቡ 2,587,002 አዳዲስ መደበኛ አክሲዮኖች በባለስልጣኑ ጸድቀዋል፡፡ ይህ ስኬት ቡና ባንክ በኢትዮጵያ የሰነደ ሙአለነዋይ ገበያ (ESX) ውስጥ በቀጣይ ለመሳተፍ ላስቀመጠው እቅድ ወሳኝ እርምጃ ነው። ባንኩ ለግልጽነት፣ ለጠንካራ የኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ለባለአክሲዮኖቹ ዘላቂ እሴት ለመፍጠር ያለውን ጠንካራ ቁርጠኝነት ያጎላ ተግባር ነው። የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሙሉጌታ ዓለማየሁ በሰጡት መግለጫ”የሰነደ ሙአለነዋያችንን በካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) በተሳካ ሁኔታ ማስመዝገባችን ለቡና ባንክ የሚያኮራ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው። ይህ ስኬታማ ክንውን የባንካችንን የወደፊት ስትራቴጂያዊ አቅጣጫ የሚያንጸባርቅ፣ የገቨርናንስ ደረጃችንን የሚያሳድግ እና የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ እያደገ ሲመጣ ለባለአክሲዮኖቻችን አዳዲስ እድሎችን የሚከፍት ነው። በዚህ ረገድ ባለአክሲዮኖቻችን እና ባለድርሻ አካላት ላሳዩን ቀጣይነት ያለው እምነት እና ድጋፍ ጥልቅ ምስጋናችንን እናቀርባለን።” ባንኩ እንዳስታወቀው ከዚህ የአክሲዮን ጉዳይ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ መረጃዎችና ማብራሪያዎች በሂደት በይፋ የሚገለጹ ይሆናል። በዚህ አጋጣሚ ቡና ባንክ ለኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ ለክቡራን ባለአክሲዮኖቹ፣ ለደንበኞቹ እና ለሁሉም አጋሮቹ ላደረጉት የማያቋርጥ ድጋፍ የከበረ ምስጋናውን ያቀርባል። ይፋዊ የአክሲየን ማህበሩን መግለጫ ሰነድ (Prospectus) ከዚህ በታች የሚገኘው ማስፈንጠሪያ በመጫን አውርደው ማንበብ ይችላሉ፡፡ 📄 መግለጫውን ያውርዱ (PDF) ለተጨማሪ መረጃ፣ እባክዎ ያነጋግሩን፦ ስልክ፦ 8501 Bunna Bank Successfully Completes Securities Registration with the Ethiopian Capital Market Authority (ECMA) (Addis Ababa, June 24, 2026) Bunna Bank S.C. is delighted to announce that it has received approval from the Ethiopian Capital Market Authority (ECMA) to register its securities. The formal registration was completed on June 23, 2026, marking a significant milestone in the Bank’s corporate development and Ethiopia’s evolving capital market. Under this registration, 61,895,598 existing ordinary shares, and the issuance of up to 2,587,002 new ordinary shares to be offered to existing shareholders, have been approved. This achievement represents an important step toward Bunna Bank’s planned participation in the Ethiopian Securities Exchange (ESX). It underscores the Bank’s strong commitment to transparency, robust corporate governance, and the creation of long-term value for its shareholders. Chief Executive Officer of Bunna Bank S.C., Ato Mulugeta Alemayehu, in his statement, stated: “The successful registration of our securities with the ECMA is a proud milestone for Bunna Bank. It reflects our forward-looking strategy, enhances our governance standards, and opens new opportunities for our shareholders as Ethiopia’s capital market matures. We remain deeply grateful to our shareholders and stakeholders for their continued trust and support.” Download the Prospectus using the link below: 📄 Download the Prospectus (PDF) Further information regarding the share management and related issues will be communicated officially in due course. At this juncture in time, Bunna Bank would like to express its sincere appreciation to the Ethiopian Capital Market Authority, its valued shareholders, customers, and all partners for their unwavering support. For more information, please contact: Telephone: 8501
ቡና ባንክ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) የሰነደ ሙአለነዋይ ምዝገባውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀቀ Read More »









