ቡና ባንክ ከደንበኞቹ ጋር ያለውን ትስስር ይበልጥ ለማጥበቅ ያለመ ልዩ የረመዳን የኢፍጣር መርሃ ግብር ረቡዕ የካቲት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሀይሌ ግራንድ ሆቴል በድምቀት አከናወነ።

በዚህ ልዩ መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ ጽ/ቤት ኃላፊ ሸህ ሙሐመድ-ዘይን ዘህረዲንን ጨምሮ ሌሎች የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ አመራሮች፣ የባንኩ ደንበኞች፣ እንዲሁም የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተው የኢፍጣር የአብሮነት ጊዜን በጋራ አሳልፈዋል።
በዚህም የባንኩ ኻዲም ከወለድ ነጻ አገልግሎት የሸሪዓ አማካሪ ቦርድ አባላትን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ከተጋባዦቹ ጋር ተገናኝተው የጋራ ቆይታ አድርገዋል። ይህ መድረክ አመራሩ ከደንበኞችና ከኃይማኖት አባቶች ጋር የጠበቀ ትስስር እንዲፈጥር፣ ፍላጎቶቻቸውን በቅርበት እንዲረዳና ተቋሙ ከፋይናንስ አገልግሎት ባለፈ ያለውን አጋርነት እንዲያረጋግጥ ምቹ አጋጣሚን ፈጥሯል።
የቡና ባንክ ቺፍ ሪቴልና ቅርንጫፍ ባንኪንግ ኢፊሰር አቶ እስክንድር ዲበኩሉ በዝግጅቱ ላይ ባስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት እንዳስታወቁት፤ ቡና ባንክ በቅርቡ ባደረገው የሥትራቴጂ ክለሳ ለኻዲም ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ትልቅ ትኩረት እንደተሰጠው አንስተዋል። ባንኩ በዚህ ረገድ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት ሰፊ ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
መርሃ ግብሩ የረመዳንን ወር እሴቶች ከማክበር ባለፈ በባንኩ አገልግሎት ተደራሽነት፣ በቀጣይ በሚኖራቸው የስራ ግንኙነት ዙሪያ ከአመራሩ ጋር ሀሳብ ለመለዋወጥ ዕድልን የፈጠረ ነበር። በዚህም በዝግጅቱ የታደሙት የእስልምና ጉዳዮች አመራሮችና ደንበኞች ባንኩ ላሳየው ተነሳሽነት ምስጋናቸውን አቅርበው፣ እንዲህ ያለው የፊት ለፊት ግንኙነት መተማመንን ለመገንባትና ባንኩ በቀጣይ ለሚቀርጻቸው ስራዎች ጠቃሚ ግብዓቶችን ለማግኘት የራሱን ሚና እንደሚጫወት ጠቅሰው ባንኩ በኻዲም ከወለድ ነጻ አገልግሎት በኩል የጀመረውን ስራ ከዚህ የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም መርሃ ግብሩ በኢፍጣር ማዕድ መጋራትና በጋራ የምስጋናና ጸሎት ስነ-ስርዓት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የኢፍጣር ዝግጅቱ ቡና ባንክ አካታችነትንና ቀጥተኛ ተሳትፎን ቅድሚያ በመስጠት ለደንበኞቹ እሴቶች ያለውን አክብሮትና ለአብሮነት ልዩ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ያሳየበት አንዱ መድረክ ሆኖ አልፏል።
Bunna Bank Hosts Grand Ramadan Iftar to Strengthen Customer Relations and Community Ties
Bunna Bank hosted a prestigious Ramadan Iftar program on Wednesday, March 4, 2026, at the Haile Grand Hotel, aimed at deepening its connection with customers and the wider community.
The event was graced by high-profile guests, including Sheikh Mohammed-Zayn Zohreddin, Head of the Ulama Council Office of the Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council, along with other senior religious leaders, valued customers, and key stakeholders.
Strategic Engagement and Leadership Presence
Senior executives of the Bank and members of the Interest-Free Banking (IFB) Sharia Advisory Board joined the guests, creating a unique opportunity for direct engagement. This platform allowed the Bank’s leadership to foster closer ties with religious figures and customers, ensuring the institution remains responsive to the community’s needs beyond traditional financial services.
Focus on “Khidmah” Interest-Free Services
During the event, Ato Eskinder Dibekulu, Chief Retail and Branch Banking Officer, delivered a welcoming message highlighting the Bank’s recent strategic revision. He emphasized that Khadim Interest-Free Banking has been identified as a top priority within the new strategy, and the Bank is aggressively working to enhance its services to satisfy the growing demands of its clients.
Collaborative Dialogue and Positive Feedback
The program went beyond a ceremonial gathering, serving as a forum for constructive dialogue regarding service accessibility and future business relations. Guests and religious leaders commended Bunna Bank for its proactive approach, noting that such face-to-face interactions are vital for building lasting trust. They further encouraged the Bank to continue strengthening its dedicated Interest-Free service, known as “Khadim.”
The evening concluded with a shared Iftar meal and a collective prayer for peace and gratitude. The event successfully demonstrated Bunna Bank’s commitment to inclusivity and its deep respect for the values and traditions of its customers, reinforcing its standing as a customer-centric and community-focused financial institution.
