Bunna Bank

Uncategorized

እየመጣን ነው 🚀

የላቀ የዲጂታል ተሞክሮን ከቀልጣፋ አገልግሎት ጋር አጣምረን ይዘንልዎ እየመጣን ነው። በጣትዎ ጫፍ የሚዘወር፣ የባንክ አገልግሎትን መልክ የሚቀይር፤ አዲስ ብስራት፣ ልዩ ነገር… ይዘን ከች ልንል ከደጃፍዎ ደርሰናል! ዝግጁ ነዎት? በቅርብ ቀን ይጠብቁን! ቡና ባንክ- የባለራዕዮች ባንክ #Bunnabank #ComingSoon #StayTuned #SomethingNew #BigUpdate  #SmartBanking #DigitalBanking

እየመጣን ነው 🚀 Read More »

በቅርብ ቀን!

የጊዜን ዋጋ ያከበረ፣ ምቾትዎን ወደ አዲስ ከፍታ የሚያሸጋግር የዲጂታል ሽግግር! 🚀 የባንክ አጠቃቀም ልምድዎን በዘመናዊ ጥበብ የሚቀይር ድንቅ ፈጠራ ይዘን በቅርብ ቀን እንመጣለን። ይጠብቁን፤ #ቡናባንክ #የዲጂታል_አብዮት #ዘመናዊነት #በቅርብ_ቀን #BunnaBank #FinTech #Innovationk

በቅርብ ቀን! Read More »

የባንክ ሒሳብዎን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር አስተሳስረዋል?

ውድ የባንካችን ደንበኞች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው መመርያ መሠረት ሁሉም ደንበኞች የባንክ አገልግሎት ለማግኘት የፋይዳ ቁጥራቸውን ከባንክ ሒሳብ ቁጥር ጋር እስከ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ማጣመር እንዳለባቸዉ ተገልጿል። በመሆኑም ማፈንጠሪያዉን በመጫን https://verifayda.bunnabanksc.com የቡና ባንክ ሒሳብዎን በቀላሉ ከቤትዎ ሆነዉ እንዲያስተሳስሩ ወይም አቅራቢያዎት ወደሚገኝ ቅርንጫፍ በመሔድ እንዲያስተሳስሩ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ ለበለጠ መረጃ ወደ ጥሪ ማዕከላችን 8501 ይደዉሉ፡፡ ቡና ባንክ- የባለራዕዮች ባንክ

የባንክ ሒሳብዎን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር አስተሳስረዋል? Read More »

ዒድ ሙባረክ! 🌙

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ቡና ባንክ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለታላቁ የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ ልባዊ ምኞቱን ይገልጻል። በዓሉ “ሙባረክ ወመይሙን” የሆነ የሰላም፣ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆንላችሁ፤ እንዲሁም ከቤተሰብ እና ከወዳጅ ዘመዶቻችሁ ጋር በበረካ የተሞላ የደስታ ጊዜ እንድታሳልፉ ከልብ እንመኛለን። ዒድ ሙባረክ! መልካም በዓል! ኻዲም ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት #EidMubarak #EidAlFitr1447 #BunnaBank #Khadim #InterestFreeBanking #Ethiopia #ዒድ_ሙባረክ #ቡና_ባንክ #የተባረከ_በዓል

ዒድ ሙባረክ! 🌙 Read More »

የሀዘን መግለጫ

የቡና ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ማኔጅመንት እና መላው ሠራተኞች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት ናዳ እና የጎርፍ አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማንን ኀዘን እየገለፅን ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን እንመኛለን፡፡

የሀዘን መግለጫ Read More »

“የአለም አቀፍ የሴቶች ቀን ንቅናቄ ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባዉ ተግባር ነዉ”- ሙሉጌታ አለማየሁ ዋና ስራ አስፈፃሚ

ማርች ፣የዓለምአቀፍ የሴቶች ወርን ምክንያት በማድረግ በባንካችን ዋና መስሪያ ቤት እና በዲስትሪክቶች እየተካሄደ ያለው ደንበኞችን የመጎብኘትና የማመስገን ፣ አዳዲስ ደንበኞችንም የመሳብና የባንኩን አገልግሎቶች የማስተዋወቅ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ተገለጸ፡፡ ከዋናው መስሪያ ቤት ከሚገኙ ልዩ ልዩ የስራ ክፍሎች በተውጣጡ ሴት አባላት የተዋቀረው የማርች 8 የባንክ አገልግሎት ማስተዋወቅና የደንበኞች ጉብኝት ቡድን ከቡና ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ሙሉጌታ አለማየሁ የስራ መመሪያ ተቀብሏል፡፡ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም በዋናው መስሪያ ቤት በተካሄደው ዝግጅት ላይ ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ ሙሉጌታ አለማየሁ ባደረጉት ንግግር ለሴቶች እኩልነት እና ተሳትፎ እዉቅና ከመስጠት በተጓዳኝ በባንካችን ሁሉም የስራ ክፍሎች በተለያዩ የስራ መደቦች ላይ ያሉ ሴት ሰራተኞች የዓለምአቀፍ ሴቶች ቀንን ምክንያት በማካሄድ ላይ ላሉት ጠንካራ እንቅስቃሴ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ለዚህ የደንበኞች ጉብኝት፣ የባንኩን አገልግሎቶች የማስተዋወቅ እና አዳዲስ ደንበኞችን የመሳብ ተግባርም ምስጋና በማቅረብ ሴት ሰራተኞች ለባንካቸው እድገትና መልካም ስም ግንባታ ላሳዩት ቁርጠኝነት አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡ በቡና ባንክ በየዓመቱ ሲካሄድ የቆየው ይህ ተግባር እያስገኘ ካለው ውጤት አንጻር ትኩረት ተሰጥቶት በስፋት ሊተገበር ይገባል ያሉት አቶ ሙሉጌታ የባንኩ ከፍተኛ አመራር ለዚህ ተግባር መሳካት ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግም ቃል ገብተዋል፡፡ “ይህ ተግባር የናንተ ቁርጠኝነትና ጥንካሬ የታየበት ከመሆኑ ባሻገር ከባንካችን እሴቶች አንዱ የሆነው “ትብብር” በስራ የተገለጸበት በመሆኑ ለባንኩ መልካም ስምና እድገት አወንታዊ ድርሻ እንዳለው እናምናለን፡፡ ስለዚህም ከመቼወም ጊዜ በላቀ ሁኔታ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል፣ የከፍተኛ አመራሩ ድጋፍም አይለያችሁም” በማለት ኢኒሺየቲቩ የከፍተኛ ማኔጅመንት እውቅና የተሰጠው መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ ዘመቻው በዋናው መስሪያ ቤት እና በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የባንኩ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች በሁሉም የሃገራችን ክልሎች ውስጥ እየተካሄደ ሲሆን ማርች ወር እስኪጠናቀቅ ድረስ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ ቡና ባንክ ይህንን የማርች ወር ምክንያት በማድረግ አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ የመንግስት ትምህርት ቤቶች በመገኘት የመማር ማስተማር ሂደቱን ሊያግዙ የሚችሉ መጽሃፍት እንዲሁም ለሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠበቂያ ፓድ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

“የአለም አቀፍ የሴቶች ቀን ንቅናቄ ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባዉ ተግባር ነዉ”- ሙሉጌታ አለማየሁ ዋና ስራ አስፈፃሚ Read More »

ቡና ባንክ ዓለም-አቀፍ የሴቶች ቀንን በልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች እያከበረ ነው

ለሴት ተማሪዎችና ለትምህርት ቤቶች ድጋፍ ይደረጋል ሴት መሪዎችን ለማብቃት ስልጠና ተካሂዷል ቡና ባንክ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (ማርች 8) ምክንያት በማድረግ፣ የሴት ሰራተኞቹን ሙያዊ ብቃት ወደ ላቀ የአመራር እርከን የሚያሸጋግር ስልጠና ከማካሄዱም በላይ፣ ተቋማዊ ማህበራዊ ሃላፊነቱን ለመወጣትም በበርካታ ትምህርት ቤቶች በመገኘት ሴት ተማሪዎችን የመደገፍና የማበረታታት እንዲሁም ለትምህርት ቤቶች እገዛ የማድረግ መርሃ ግብርም ያካሂዳል፡፡ ከዚህ ባሻገርም የባንኩን እና አጋሮቹን ግንኙነት የሚያጎለብት የደንበኞች ጉብኝትና የአገልግሎት ማስፋት ዘመቻ በይፋ አስጀምሯል። ባንኩ ከካፒታል የፋይናንሺያል የልህቀት ማዕከል (CFEC) ጋር በመተባበር ከየካቲት 25 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ለሁለት ቀናት ያካሄደው “የሴቶች አመራርና የሙያ እድገት” ስልጠና፤ ከዋናው መስሪያ ቤት እስከ ቅርንጫፍ ያሉ ሴት አመራር ሰራተኞች በስትራቴጂካዊ ውሳኔ አሰጣጥ፣ በተፅዕኖ ፈጣሪ ተግባቦትና በራስ መተማመን ዙሪያ የላቀ ክህሎት እንዲጨብጡ አስችሏል። ይህ መርሃ ግብር ተሳታፊዎቹ ለቀጣይ ሶስት ዓመታት የሚሆን ግልጽ የሙያ እድገት ራዕይ እንዲሰንቁ ከማድረጉም ባለፈ፣ ሴቶች ያላቸውን እምቅ አቅም ለተቋማዊ ስኬት እንዲያውሉ የሚያነቃቃ መድረክ ሆኖ ተጠናቋል። ይህንኑ የውስጥ አቅም ግንባታ መነቃቃት ወደ ደንበኞች አገልግሎት በማሸጋገር፣ ባንኩ “የማርች 8 የደንበኞች ግንኙነት እና የሽያጭ ዘመቻ” በሚል ታላቅ እንቅስቃሴ መጀመሩን በይፋ አብስሯል። ይህ ዘመቻ ማርች 8ን አጋር ደንበኞችን በማመመስገንና ግንኙነቶቻችን ይበልጥ በማጠናከር ለማክበር የታለመ ሲሆን፤ በተለይም በችርቻሮ (Retail)፣ በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች (SME) እንዲሁም በኮርፖሬት የደንበኞች ዘርፍ ላይ ልዩ ትኩረት ያደርጋል። ዘመቻው የዲጂታል ባንክ አገልግሎት አጠቃቀምን ማሳደግ፣ አዳዲስ ደንበኞችን ማፍራት እና የባንኩን የማህበራዊ ሚዲያ ተደራሽነት ከማጠናከር ጎን ለጎን በተለያዩ ትምህርት ቤቶች በመገኘት የትምህርት አጋዠ ቁሳቁሶችን እገዛና ሴት ተማሪዎችን ለማበረታታትም ልዩ ልዩ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡ በአጠቃላይ ቡና ባንክ የሴት ሰራተኞቹን የውሳኔ ሰጪነት ሚና ማጎልበትን ከቢዝነስ ስኬቱ ጋር በማስተሳሰር፣ ለሥርዓተ-ጾታ እኩልነትና ለተቋማዊ እድገት ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተግባር እያሳየ ይገኛል። ባንኩ የሰራተኞቹን ብቃት በማሳደግና የደንበኞቹን እምነት በማዳበር፣ ውጤታማ የሀብት ማሰባሰብ ስራንና ዘላቂ የንግድ እድገትን ለማረጋገጥ አስፈላጊውን ድጋፍና ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠሩን እንደሚቀጥልም አስታውቋል፡፡

ቡና ባንክ ዓለም-አቀፍ የሴቶች ቀንን በልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች እያከበረ ነው Read More »

ቡና ባንክ የደንበኞች ግንኙነቱን የሚያጠናክር የረመዳን የኢፍጣር መርሃ ግብር አካሄደ

ቡና ባንክ ከደንበኞቹ ጋር ያለውን ትስስር ይበልጥ ለማጥበቅ ያለመ ልዩ የረመዳን የኢፍጣር መርሃ ግብር ረቡዕ የካቲት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሀይሌ ግራንድ ሆቴል በድምቀት አከናወነ። በዚህ ልዩ መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ ጽ/ቤት ኃላፊ ሸህ ሙሐመድ-ዘይን ዘህረዲንን ጨምሮ ሌሎች የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ አመራሮች፣ የባንኩ ደንበኞች፣ እንዲሁም የተለያዩ አጋር አካላት ተገኝተው የኢፍጣር የአብሮነት ጊዜን በጋራ አሳልፈዋል። በዚህም የባንኩ ኻዲም ከወለድ ነጻ አገልግሎት የሸሪዓ አማካሪ ቦርድ አባላትን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ከተጋባዦቹ ጋር ተገናኝተው የጋራ ቆይታ አድርገዋል። ይህ መድረክ አመራሩ ከደንበኞችና ከኃይማኖት አባቶች ጋር የጠበቀ ትስስር እንዲፈጥር፣ ፍላጎቶቻቸውን በቅርበት እንዲረዳና ተቋሙ ከፋይናንስ አገልግሎት ባለፈ ያለውን አጋርነት እንዲያረጋግጥ ምቹ አጋጣሚን ፈጥሯል። የቡና ባንክ ቺፍ ሪቴልና ቅርንጫፍ ባንኪንግ ኢፊሰር አቶ እስክንድር ዲበኩሉ በዝግጅቱ ላይ ባስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት እንዳስታወቁት፤ ቡና ባንክ በቅርቡ ባደረገው የሥትራቴጂ ክለሳ ለኻዲም ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ትልቅ ትኩረት እንደተሰጠው አንስተዋል። ባንኩ በዚህ ረገድ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት ሰፊ ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ መርሃ ግብሩ የረመዳንን ወር እሴቶች ከማክበር ባለፈ በባንኩ አገልግሎት ተደራሽነት፣ በቀጣይ በሚኖራቸው የስራ ግንኙነት ዙሪያ ከአመራሩ ጋር ሀሳብ ለመለዋወጥ ዕድልን የፈጠረ ነበር። በዚህም በዝግጅቱ የታደሙት የእስልምና ጉዳዮች አመራሮችና ደንበኞች ባንኩ ላሳየው ተነሳሽነት ምስጋናቸውን አቅርበው፣ እንዲህ ያለው የፊት ለፊት ግንኙነት መተማመንን ለመገንባትና ባንኩ በቀጣይ ለሚቀርጻቸው ስራዎች ጠቃሚ ግብዓቶችን ለማግኘት የራሱን ሚና እንደሚጫወት ጠቅሰው ባንኩ በኻዲም ከወለድ ነጻ አገልግሎት በኩል የጀመረውን ስራ ከዚህ የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በመጨረሻም መርሃ ግብሩ በኢፍጣር ማዕድ መጋራትና በጋራ የምስጋናና ጸሎት ስነ-ስርዓት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የኢፍጣር ዝግጅቱ ቡና ባንክ አካታችነትንና ቀጥተኛ ተሳትፎን ቅድሚያ በመስጠት ለደንበኞቹ እሴቶች ያለውን አክብሮትና ለአብሮነት ልዩ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ያሳየበት አንዱ መድረክ ሆኖ አልፏል።   Bunna Bank Hosts Grand Ramadan Iftar to Strengthen Customer Relations and Community Ties Bunna Bank hosted a prestigious Ramadan Iftar program on Wednesday, March 4, 2026, at the Haile Grand Hotel, aimed at deepening its connection with customers and the wider community. The event was graced by high-profile guests, including Sheikh Mohammed-Zayn Zohreddin, Head of the Ulama Council Office of the Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council, along with other senior religious leaders, valued customers, and key stakeholders. Strategic Engagement and Leadership Presence Senior executives of the Bank and members of the Interest-Free Banking (IFB) Sharia Advisory Board joined the guests, creating a unique opportunity for direct engagement. This platform allowed the Bank’s leadership to foster closer ties with religious figures and customers, ensuring the institution remains responsive to the community’s needs beyond traditional financial services. Focus on “Khidmah” Interest-Free Services During the event, Ato Eskinder Dibekulu, Chief Retail and Branch Banking Officer, delivered a welcoming message highlighting the Bank’s recent strategic revision. He emphasized that Khadim Interest-Free Banking has been identified as a top priority within the new strategy, and the Bank is aggressively working to enhance its services to satisfy the growing demands of its clients. Collaborative Dialogue and Positive Feedback The program went beyond a ceremonial gathering, serving as a forum for constructive dialogue regarding service accessibility and future business relations. Guests and religious leaders commended Bunna Bank for its proactive approach, noting that such face-to-face interactions are vital for building lasting trust. They further encouraged the Bank to continue strengthening its dedicated Interest-Free service, known as “Khadim.” The evening concluded with a shared Iftar meal and a collective prayer for peace and gratitude. The event successfully demonstrated Bunna Bank’s commitment to inclusivity and its deep respect for the values and traditions of its customers, reinforcing its standing as a customer-centric and community-focused financial institution.

ቡና ባንክ የደንበኞች ግንኙነቱን የሚያጠናክር የረመዳን የኢፍጣር መርሃ ግብር አካሄደ Read More »

ረመዷን ከሪም! 🌙💫

የረመዷን ጉዞ ተጋምሶ ወደ መጨረሻዎቹ የብርታት ቀናት እያሸጋገረን ነው። ከምህረትና ይቅርታ… ወደ ታላቁ የነጻነት ደጃፍ — ኢትቁን ሚነን-ናር — ተቃርበናል! 🌙 ቡና ባንክ በ”ኻዲም” ከወለድ ነፃ አገልግሎቱ፣ እምነትዎንና ራዕይዎን አክብሮ በኺድማ ያጅብዎታል። ዘመናችሁ በበረካና በስኬት የተሞላ ይሁን! ረመዷን ከሪም! ✨ ቡና ባንክ — የባለራዕዮች ባንክ!

ረመዷን ከሪም! 🌙💫 Read More »

This will close in 0 seconds

Open Your Bank Account Today!

አካውንት ይክፈቱ የክፍያ ካርድዎን ያዝዙ ፣ ፈጣን አገልግሎት ማግኘት ይጀምሩ! ዛሬውኑ ይቀላቀሉን!

Open Bunna Account

You cannot copy content of this page